What makes you interested?!

Here are some thoughts, when we were younger anything that our older brother, sister or friend act, say or does keeps our mind for a while. Trying to do exactly what we have seen “monkey see monkey do”. We think its cool we do not process the consequence.

Then we get older success is our drive we want to achieve something. Anything but that can put as in spotlight. So we can showoff! “I did it”. Me is the the center. We plan work hard we make it happen,

Then what? Tuff question now what? Difficult to explain, it seems no one will understand. Things that looks interesting are not interesting any more, thing that looks unreachable are under the foot now: then what?

Have you ever stuck on this moment? May be yes may be not, if you are here welcome to rearranging your vision if you not here yet, wait for it you will get there!

Life is more beautiful and fresh very moment when the center of it is not “ME”. Learn that in life her self, joyful moment are stack with others “WE” bring more fun that me. Together we are Strong, fresh and alive!

Dream for others strive to support be consistent. Some one thought me as a teenage girl the “the secret of greatness is taking responsibility!” It’s stay with me. So find your interest in helping others you will never get bord with it.

Netsanet

The price of greatness is responsibility.” – Winston Churchill.

እውነትን መናገር

በመንገድ ላይ ካየሁት ተነስቼ ብቻ ባወራ በእርግጥ የልምዴን እናገር ይሆናል ይህ ብቻ ግን የታሪክን ሙሉ እውነት አይገልፅም። አንዳንዱን እንደውም ስለረሳሁት ወይንም ላያስፈልግ ይችላል ከሚል ግምት ልዘለው እችላለሁ። ገጥሞአችሁ ያውቅ ይሆን የሆነ የምታውቁት ሰውን መንገድ ላይ አይታችሁት: ምን አልባት በርቀት ወይም በችኮላ ይሆንባችሁና ሳታናግሩት አልፋችሁ። ያን ሰው ስታገኙት በዚህ ቀን እዚህ ቦታ አየሁህ ስትሉ ያሰው በፍፁም በዛ ስፍራ እንዳልነበር ሲያስረዳችሁ? ወይንም እንዳያችሁት ስልክ ደውላችሁ እያየሁህ እኛ ለፍከኝ እንዲህ ቦታነኝ ስትሉ ያሰው ጭራስ ሌላ ክፍል ስፍራ መሆኑን ሲያረጋግጥላችሁ። ታዲያ ምን ትንሽ ፈጠረ? ያያችሁት ማንን ነው? ብዚ ጊዜ እንደነዚህ አይነት አጋጣሚዎችን ዝም ብለን እንደ ተራ እናልፋቸዋለን። ነገርግን በእርግጥ ብናስተውላቸው ሌላ እውነት አላቸው ተምረባቸው እንድናልፍ የሚጠበቅ እውነት። ያየነው ብቻውን በቂ አይደለም።

አስታውሳለሁ የህግ መፅሃፍትን አገላብጥ ዘንድ እድል በነበረኝ ወቅት መምህራችን እንዲህ ይል ነበር “መስመሩ ላይ ያለውን ብቻ እኛ ታንብቡ ከመስመሩ በታች፣ ከመስመሩ በላይ ከመስመሩ በስተጀርባ የተፃፈውን ፈልጉ” እንዴት ያለ ትእዛዝ ነው? እኔ “የተፃፈውን እንጂ ያልተፃፈውን ከየት አምጥተን እናነባለን?” ያው መምህር ስለሚከበር በፊቱ አላጉረመረምኩም በልቤ እንጂ ።

በእርግጥም እውነት ለካ እንዲህ ናት አንዳንዴ ፊትለፊት ያለው የተገለጠው ብቻ ሳይሆን ያልተገለጠ የሚመስል ነገርግን ግልጥ የሚመስለውን የሚመራ እና የሚያስተናብር እውነት አለ።

በህግ ትምህርት ላይ ህጉ ምን ይላል የሚለውን ለማየት ህግ አውጪዎቹ እነማን ናቸው? መቼ ነው ይህግ የወጣው? በዚህ ህግ መውጣት ጊዜ ምን ምን አይነት ክርክሮች ውይይቶች ተደርገው ነበር? ይህ ከመውጣቱ በፊት በምን ሁኔታ ነበር ጉዳዩ የሚታየው? ወደፊትስ ሊሸፍን የሚፈልገው ክልል አለወይ? እንግዲህ አንድ ህግ የሚለውን ለማወቅ ነው ይህ ሁሉ ምርምር: በእርግጥም በጥንቃቄ መረዳቱ ለሎሎች ህይወት ተፅዕኖ መፍጠር የሚያስችል አቅም ነውና ትክክለኛው ሃሳብ ማግኘት ግድያደርገዋል።

በህይወት ውስጥም እውነትን መፈለግ ከዚህ የባሰ ዝርዝር እይታ ይጠይቃክ ። ፊታችን ላይ እየሆነ ያለውን ብቻ ሳይሆን ከዛ አልፈን ማየት ይጠይቃል። ግለሰቦችን በውሳኔዎቻቸው እንዳንፈርፍባቸው ወይም የራሳችን እርምጃዎች ጠባብ በሆነ መንገድ ውስጥ እንዳይገኝ እውነትን መከታተል መልካም ነው።

የሐንስ 8:32 እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል፡ አላቸው።