የመወለዴ ክፍል

ብዙ ጊዜ ወደ አምላካችን ስንጠጋ ወይንም በራልኝ፣ ተረዳሁ ፣ ገብቶኛል እያልን ስንል የገባን ምንአልባትም የጠቅላላውን እውነት ጥቂቱን ብቻ መሆኑን ለማየት ጊዜ ይወስድብናል ወይንም ደግሞ የዛን እይታ ትልቅ ክፍል እንዳለው ለማመን ይከብደናል። እውነቱ ግን ይህ ነው።

ከእውቀት ከፍለን እናውቃለን

ምንም ያክል ሊቅ ጠቢብ ብንሆን ወይንም የሃይማኖት ጥናት ብናደርግ አምላክ ታውቆ አይጨረስም። አምላክ አምላክ ነውና እንክዋን እርሱን በሙሉ አውቆ ለመጨረስ የፈጠረውን አንድ ፍጥረት እንኳን ለማጥናት ዘመናት ይፈጃል። ለዚህ አይደል ሳይንቲስቶች ዛሬም ስራ ያላቸው! ፍጥረት እስካለ የሚጠና ነገር ይኖራልና።

ወደ ተነሳሁበት ልመለስና እውነት እውነት ግን ምን ያክል ነው የበራልን? ምን ያክል ነው የተረዳነው? የአምላክ ልጅ ነኝ ብሎ አንድሰው በምድር እየተመላለሰ ነገርግን አንድም የአባቱ ሁኔታ በእርሱ ላይ መገለጥ ካልቻለ በእርግጥ ልጅ ነው ማለት እንችላለን? ይህን ሁኔታ በምን ገምግመን ነው አዎ የአምላክ ልጅ ነው ማለት የምንችለው? ለምሳሌ አንድ ልጅ አባቱን በመልክ ሊመስል ይችላል ቁርጥ አባቱን ነው ይላሉ የአገሬ ሰዎች። ወይንም የአባቱን ሃብት ያለመከልከል ሲጠቀም ብናይ አለያ ይህ ሰው ጥፋት አጥፍቶ ሲይዝ አባቱ ዋስ ከፍሎ ሲያስፈታው ስናይ ከሌላው ሰው የሚለይበት ነገር እናያከን። ምንአልባትም እንክዋን ያለ አግባብ ያባቱን ሃብት ቢበትን አንተ እንዴት በተንክ ብሎ የሚጠይቅ የውጪ ሃይል የለም። ምክንያቱም ይህ በአባትና ልጅ መካከል የሚደረግ ውይይት ነውና ሌላው ሰው አያገባውም።

ታዲያ ግን ለተቀበሉት ሁሉ ግን በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የልጅነት ስልጣን ሰጣቸው ተብሎ ተፅፎ ሳለ ። ልጅ ነኝ የሚለው ጉዳይ ምንው ለብዙ ዳግም ተወላጅ ቃል ብቻ ሆነ? ለዚህ ነው ጥያቄው ያነሳሁን የተገለጠልን በከፊል ብቻ ነው መሰል? ልጅ ከሆንክ/ሽ አዲስ ዘር ውስጥ ገብተሃል/ሻል። አባት ያለውን ሁሉ ነህ/ሽ።

ይህ እውነት ከሲኦል ማምለጥ አንዱ ጅማሬ ሲሆን ደግሞም አምላክን መምሰል ፍፃሜው ነው። በእነዚህ ሁለት ጥጎች ውስጥ የትኛው ጋር ደርሳችሁ ይሆን?

ኢየሱስም ደግሞ አላቸው፡— እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እኔ የበጎች በር ነኝ።

Then said Jesus unto them again, Verily, verily, I say unto you, I am the door of the sheep.

ዮሐንስ 10:7

ነፃነት Nov, 19 2022

ወደ ኮሌጅ ልጅን መላክ

የሰባት አመት ልጄን የበጋ ወራት የመፅሃፍ ቅዱስ ካምፕ ላደርሰው ሻንጣውን ይዞ ከቤት ስንወጣ ነፍሴ ድንገት ከውስጤ የወጣች መሰለኝ የምንኖርበትን ቤት በር እንክዋን አልዘጋሁም ልጄ ላይ አፍጥጬ ቀረሁ። ጊዜና ቦታ በማይገድበው ምእናብ ልጄን ኮሌጅ ሲሄድ አየሁት ፣ በኮሌጅ ትምህርት ቢዚ ሲሆን ሊያወራኝ እንክዋ ጊዜ የለኝም ሲል። ጊዜ ፍጥነቱ!!

ትምህርት ጨርሶ እቤት ይመጣል ብዬ ላስብ ስሞክር አይ አይደለም ስራ ይይዘዋል ከአገር አገር፣ ከቢሮ ቢሮ፣ ታላላቅ ጉዳዮችን ሊፈፅም ይሮጣል። ልጄ ናፈቀኝ!!

እንዴ እንዴ በቃ እንዲህ ነው ድንገት ሳልዘጋጅ ልጄ ከእጄ የሚወጣው? የልጄ በፍጥነት ማደግ ማስረጃ ሆነው ከፊቴ ተደረደሩ: እውነት ነው ጨቅላ ሆኖ እጄ ላይ የተንከባለለበት ቀን እና ዛሬ የደረሰበት እድሜ በምን ጊዜ እንደደረሰ በትክክል አይገባኝም በጣም ቸኩሎብኛል።

አውቃለሁ ይህ ብላቴና በጎበዝ እጅ እንዳለ ቀስት ነው ተወርውሮ አላማውን ይመታል። ደግሞም ይወጣል ይወርሳል ያሸንፋል።

ለእኔ ግን ዛሬ ናፍቆት በሆዴ ውስጥ ገባ ልጄ እንዳይሄድብኝ ፈለኩ: አይን አይኑን አያለሁ የያዘውን ሻንጣ አያለሁ። ላስቀረው? እድሜው ገናነው ምን አስቸኮለኝ? ይቅር እቤት ውስጥ ይቀመጥ ልቤ አማራጭ ሰጠኝ። አይ ይሄማ ለእድገቱ ውሳኝ ነው ዛሬ ህይወቱ ላይ የዘራሁት ነው ነገ ተፅእኖ የሚያመጣው። ክርክር ውስጥ ገባሁ. “ማም!! ” ልጄ ቀሰቀሰኝ : “በር እየዘጋሁ ነው መጣሁ” መለስኩለት። ምን ሆናለች ዛሬ እናቴ ሳይል አይቀርም አስተያየቱ ያስታውቃል

ተንደርድሬ አቀፍኩት ሳምኩት፣ እወድሃለሁ እሺ እሺ!፣ “እ” መልሱ ነበር። ” ቃል ግባልኝ” ጠያቂ ሆንኩ. “ዋት?” ነገሬ የገረመው ልጄ. “አሁን እኮ ትልቅ ልትሆን ነው ኮሌጅ ልትገባ ልትማር ስራ ልትይዝ በቃ ጊዜ አይኖርህም።” ልጄ የማወራውን በግልፅ ይግባው አይግባው አላውቅም ነገር ግን የልቤን ጭንቀት መተንፈስ ቀጠልኩ። ስለዚህ አደራ እንድትደውልልኝ እሺ “ኖ!! አም ጎነ ቢ ቢዚ” የልጄ መልስ ነበር። “ትናፍቀኛለህ እኮ እባክህ?” “ማም!” ስምንት አመት እንክዋን ካልሞላው ልጄ ጋር ድርድር ያዝኩ ቀኑ ሲደርስ ከማለቅስ በጊዜ ብለምን ይሻለል ብዬ።

ምሳሌ 22: 6 ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም።

በዚህ ውስጥ ነፍሴ ሌላ ነገር አስተዋለች በልዩ ልዩ ነገር ዛሬ ቢዚ ሆኜ የማይመለስ ውድ ጊዜ ከልጄጋር ማሳለፌን እንዳያመልጠኝ ፣ እንድደሰትበት ዋጋ እንድ ሰጠው። ነገ የልጄ ቀን ነው እርሱ ተራውን የሚሮጥበት የሚወርስበት ነውና የእርሱን ጊዜ መሻማት ሳይሆን የእኔን ጊዜ በአግባቡ መጠቀምን ተማርኩ።

እየተነጋገርን አሳንሳር ውስጥ ገብተን መኪናዬ ጋር ደረስን። አምላኬ ታማኝ እና እውነተኛ ነው ታላቅና ሃይለኛ ነገር በዚህ ልጅ ያደርጋል። ቀኑ ሲደርስ እኔንም ይረዳል።

እናንተስ ልጃችሁ የቱጋር ነው ያሉት? የትስ እንዲዱ ታያላችሁ?

ነፃነት

What makes you interested?!

Here are some thoughts, when we were younger anything that our older brother, sister or friend act, say or does keeps our mind for a while. Trying to do exactly what we have seen “monkey see monkey do”. We think its cool we do not process the consequence.

Then we get older success is our drive we want to achieve something. Anything but that can put as in spotlight. So we can showoff! “I did it”. Me is the the center. We plan work hard we make it happen,

Then what? Tuff question now what? Difficult to explain, it seems no one will understand. Things that looks interesting are not interesting any more, thing that looks unreachable are under the foot now: then what?

Have you ever stuck on this moment? May be yes may be not, if you are here welcome to rearranging your vision if you not here yet, wait for it you will get there!

Life is more beautiful and fresh very moment when the center of it is not “ME”. Learn that in life her self, joyful moment are stack with others “WE” bring more fun that me. Together we are Strong, fresh and alive!

Dream for others strive to support be consistent. Some one thought me as a teenage girl the “the secret of greatness is taking responsibility!” It’s stay with me. So find your interest in helping others you will never get bord with it.

Netsanet

The price of greatness is responsibility.” – Winston Churchill.

ስራ ላይ ሆኜ ያገኘኛል

ምን እጃችሁ ላይ አለ? እርሱ እመጣለሁ ብሎ የዘገየ በሚመስለበት በዚህ ሰአት እርሱ የሚከፍለውን ደሞዝ ይዞ ሲመጣ ማንን ያገኝ ይሆን ምንስ በእጅ ላይ ይገኝ ይሆን?

ስራ የተሰጥን እንድናበጅ እንድናስተዳድር ተንከባካቢ እንድንሆን እንድን ጠብቅ ነው ይህ ከሰማይ ያለው ሃሳብ ነው። መስተዳድር ተብሎ በተሰጠህ ላይ ምን ያክል ሰርተህ ይሆን? በአንተ በእንቺ ውስጥ ስራ ግን ምን አይነት ትርጉም ይኖረው ይሆን? ምን አይነትስ ስራስ እየሰራሽ አለቃሽ ያገኝሽ ይሆን?

ገንዘብ መውደድ የሃጥያት ሁሉ ስር ነውና የምናሳድደውን ብናውቅ መልካም ነው ገንዛብ ለማግኘት ፪፬ ሰአት ስትሮጥ ውለህ አድረህ ድንገት የደረስክበት ሲመስልክ ከእጅ አፈትልኮ እንደ ምርጥ እየመሰለ በብዙ ምኞት እና ሃሳብ በማናወዝ ከተፈጠርክለት የመግዛት ስፍራ ያወርድህና ባርያ ያደግሃል። አለቃህንም በትጋት እንዳትጠብቅ ያሳስታል።

ትዳር ብዙ ወገኖኝ በብቸኝነት ዘመናቸው ፈጣን ሯጭ ናቸው ትዳር ውስጥ ሲገባ ቀዝቀዝ ማለት መጀመሩ መልካም ቢመስልም ለብዙዎች ግን ጭልጥ ብሎ መተኛ ይሆናል። ንቃ ንቂ ትዳርሽ በእርግጥ በጌታ ፊት የምትሸለሚበት ቢሆንም የእርሱን ስራ ግን እርግፍ አድርገህ /ሽ እንድትተዊው አልነበረም የሰጠህ።

ድካም በሁሉ ቤት ያንኳኳል ካለብን ጫና ወይም ከወደቀ አለም ግፊያ የተነሳ እርሱም ቢሆን ግን ከመንቃትና ከመጠበቅ አይከለክልም

ምንድን ይሆን ያደከመህ ስራህን እንዳትሰራ ያስደረገህ? እኔ ግን ድንገት በክብሩ ቢገለጥ ስራ ላይ ሆኜ ያገኘኛል አታንቀላፋ አታንቀላፊ ጊዜው በረዘመ ጊዜ ተስፍሽ የበለጠ ይታደድ እንጂ አትዘናጊ።

ዘፍጥረት 1:28                                               እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው፡— ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥ ግዙአትም፤ የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ግዙአቸው።

ነፃነት


			

ይቅርታን መቀበል

ሰዎች መጥተው ይቅርታ ቢጠይቁአችሁ መልሳችሁ ምን ይሆን?

ሰዎችን ይቅር ብዬሃለሁ ማለትና መተው መታደል ነው። በአንድ ወቅት እንዲህ ሆነ እግዚአብሔር ይቅርታን እሚያስተምረኝ ዘመን ነበር እና የተለያዩ ሰዎችን ይቅርታ እንድጠይቅ ያስተምረኛል እናም አንድ ሰውን ይቅርታ መጠየቅ ነበረብኝ ስለዚህ ሄድኩ ሳገኘው ይቅርታ እንድታደርግልኝ ፈልጌ ነው ይቅርታ አልኩ። ያሰው በጣም ተናደደ የማይሆን የማይሆን ነገሮችን ተናገረ ጭራሽ ነገሩ የባሰ የሆነ መሰለ። በዚያን ወቅት እኔ ብዙም አልጨነቀኝም ነገሩን ተቀበለው አልተቀበለው ሳይሆን እኔ ሄጄ ይቅርታ ማለቴ ብቻ ነበር ግዴታ አድርጌ ያሰብኩት። ምንአልባት አሁን ቢሆን ለዛ ሰው የተለየ መራራትና ሃዘኔታ ግድ ማለት ይበዛልኝ ነበር።

ጊዜያት አለፉ በተለያየ ጊዜ ይቅርታ መጠየቅና ይቅር ማለት የህይወቴ ክፍል ሆኖ ቀረ ። ከሰው ጋር ስንኖር ሊያሳዝኑን ቢችሉ ይቅር ብሎ መተውን የመሰለ ልብን የሚያሳርፍ ነገር እንደሌለ አውቄያለሁ። የሁለችን አይኖች በተከፈቱና ይህን ማየት በቻልን። ከይቅርታ የሚበልጥ የነፃ መውጣት ሚስጥር የለም።

እናም ዛሬ ይህን የምፅፍበት ምክንያት መጣ የኔ የሆነሰው አሳዝኖኝ ነበርና ትንሽ ከፍቶኛል ታዲታ ያሰው ደውሎ ይቅርታ በቀደም አሳዘንኩሽ ማለት፡ የሚሰማው ጆሮዬ ንግግሩን በትክክል መስማቱን ማረጋገጥ ፈለኩኝ፡ ማመን ከበደኝ ፣ ቀልድ መሰለኝ እንደውም ነገሩ በሆነ ሰአት የተሰማኝ ህመም ተመለሰ ፡ ይህ ቀልድ ነው እውነት? አይምሮዮ በሰኮንዶች ውስጥ ብዙ አሰበ ። እየተነገረ ያለው የይቅርታ ቃል ይልቅ የደረሰብኝ ሃዘን ገዝፎ ለመውጣት ታገለኝ። የሆነብኝን ነገር መናገር ጀመርኩ ወዲያው ግን ተመለስኩ ይቅርታ በመተው እንጂ በደልን በመቁጠር አይፈታም። እሺ ይቅር ብያለሁ ተውኩ አልኩ።

ምን አልባት አንተ አንቺ ይህን ስታነቢ በፍፁም ይቅር አልልም ያልሽበት ጉዳይ ይኖር ይሆን? ያንን ሰው ወይንም ወቅት በሃሳብ ላይ ሲመጣ ህመም ይሰማል? ሃዘን፡ ንዴት ይፈራረቅ ይሆን? እንግዲያው መፍትሄው አንድ ነው ሌላ መድሃኒት የለውም ይቅርታ ይባላል።

ማቲዎስ 5:7
የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና

እናም ሰውን ይቅርታ መጠየቅ መታደል ነው አንድ አንዴ ነገሩ የባሰ ቢመስል እንክዋን መንፈስ ልብን እንዲጠግን ተስፋ አድርጎ ማለፍ ያስፈልጋል። አሁን ያሰው ያኔ ይቅርታ ስጠይቀው ለምን እንደተናደደብኝ ገብቶኛል ለዛ ሰው አብዝቼ መፀለይ ነበረብኝ በራሱ አቅም ይቅርታን ሊሰጥ አይችልም እና አልፈርድበትም። ምን አልባት ዳግም ባገኘው ያን ሰው ሰላም በዝቶለት እንዳይ እመናለሁ።

በህይወት ውስጥ እጅግ አስፈላጊ ነገር፡ ግን ለብዙዎች የሚከብድ ቢኖር ይቅርታ ነው። አምላክ እራሱ በአካል መጥቶ ማስተማር የተጠበቀበት ለዚሁ ይመስለኛል። እናንተስ ምን ትላላችሁ ይቅርታ ጠይቃችሁ አለያ ተጠይቃችሁ ታውቁ ይሆን

Do you really deserve it all?

Is it really you are entitled to get everything? I usually here some speakers saying you are! You can do anything! You deserve it!

Really? I question that?

Are you trying to ascend to heavens to be like god’s or you know your places, you know you are placed to domain not to own!

There is clear fine line between bousting up to reach heaven , and humbly receiving the gift., where are you standing? Which one are you?

What you deserve is punishment, “for the wage of sin is death”. But someone took that payment for you. That put you free man!.

Because of this you are allowed to share the gifts. You did noting to create them!, they were made by someone, every living things and non living things around you looks up to the creater, they are a countable to Him. They don’t answer to you they only answer to Him, it is amazing how “HE” deleget things, As a free man you are responsible to take good care for them, because of the job description some power and Authority is imposed on you. this is why nature will respond to you.


ሁሉ ነገር የተሰጠን ከምህረት እጁ ውስጥ እንጂ ይገባን ዘንድ ያደረግነው አንዳች ነገር የለም። ሁሉ በእርሱ ለእርሱ የሆነው እንዲሁ በነፃ ሰጠን እንጂ።

ለአንተ ወይንም ለአንቺ ጥቅም ብቻ የሚውል የተሰጠ አዲስ ስልጣን የለም። ነገርግን የመንግስቱን ክብር ግርማ ወግ ስርአት ለመግለጥ ተሰጠ እንጂ ።

ሁሉ ይታዘዝለት ዘንድ የተቻለው ያንኑ ስልጣኑን አካፈለን : ይህ ማለት ግን እንድንጎርር ወይንም እንድንኩራራ ሳይሆን እርሱ በልቡ ትሁት ነው እና የእርሱን እግር ተከትለን መልካሙን የመንግስት አስተዳደር እንድንፈፅም ነው።

አንድ ግለሰብ እራሱን ብቻ እያሰበ ስልጣን ተሰጥቶኛል አቅም አለኝ ወዘተ — ቢለፈልፍ ኪሳራ ነው። ወይንም ደግሞ ጉዳዩ ከዘላለም መንግስት ጋር ግንኙነት የለውም። ይህ የተለቀቀው ኃይል መንግስትን ለመግለጥ ነውና ፡ የሰማይ መንግስት ደግሞ ሁሉን ይገዛል ለባሮቹም የተካፈለው ስልጣን ከሃላፊነት ጋር ነው

እግዚአብሔር የሰጠኝን ምህረት፣ ህይወት ፣ ስልጣን እንዲህ በቀልድ አልይዘውም በትህትና እና እርሱን በመፍራት እንጂ

እውነትን መናገር

በመንገድ ላይ ካየሁት ተነስቼ ብቻ ባወራ በእርግጥ የልምዴን እናገር ይሆናል ይህ ብቻ ግን የታሪክን ሙሉ እውነት አይገልፅም። አንዳንዱን እንደውም ስለረሳሁት ወይንም ላያስፈልግ ይችላል ከሚል ግምት ልዘለው እችላለሁ። ገጥሞአችሁ ያውቅ ይሆን የሆነ የምታውቁት ሰውን መንገድ ላይ አይታችሁት: ምን አልባት በርቀት ወይም በችኮላ ይሆንባችሁና ሳታናግሩት አልፋችሁ። ያን ሰው ስታገኙት በዚህ ቀን እዚህ ቦታ አየሁህ ስትሉ ያሰው በፍፁም በዛ ስፍራ እንዳልነበር ሲያስረዳችሁ? ወይንም እንዳያችሁት ስልክ ደውላችሁ እያየሁህ እኛ ለፍከኝ እንዲህ ቦታነኝ ስትሉ ያሰው ጭራስ ሌላ ክፍል ስፍራ መሆኑን ሲያረጋግጥላችሁ። ታዲያ ምን ትንሽ ፈጠረ? ያያችሁት ማንን ነው? ብዚ ጊዜ እንደነዚህ አይነት አጋጣሚዎችን ዝም ብለን እንደ ተራ እናልፋቸዋለን። ነገርግን በእርግጥ ብናስተውላቸው ሌላ እውነት አላቸው ተምረባቸው እንድናልፍ የሚጠበቅ እውነት። ያየነው ብቻውን በቂ አይደለም።

አስታውሳለሁ የህግ መፅሃፍትን አገላብጥ ዘንድ እድል በነበረኝ ወቅት መምህራችን እንዲህ ይል ነበር “መስመሩ ላይ ያለውን ብቻ እኛ ታንብቡ ከመስመሩ በታች፣ ከመስመሩ በላይ ከመስመሩ በስተጀርባ የተፃፈውን ፈልጉ” እንዴት ያለ ትእዛዝ ነው? እኔ “የተፃፈውን እንጂ ያልተፃፈውን ከየት አምጥተን እናነባለን?” ያው መምህር ስለሚከበር በፊቱ አላጉረመረምኩም በልቤ እንጂ ።

በእርግጥም እውነት ለካ እንዲህ ናት አንዳንዴ ፊትለፊት ያለው የተገለጠው ብቻ ሳይሆን ያልተገለጠ የሚመስል ነገርግን ግልጥ የሚመስለውን የሚመራ እና የሚያስተናብር እውነት አለ።

በህግ ትምህርት ላይ ህጉ ምን ይላል የሚለውን ለማየት ህግ አውጪዎቹ እነማን ናቸው? መቼ ነው ይህግ የወጣው? በዚህ ህግ መውጣት ጊዜ ምን ምን አይነት ክርክሮች ውይይቶች ተደርገው ነበር? ይህ ከመውጣቱ በፊት በምን ሁኔታ ነበር ጉዳዩ የሚታየው? ወደፊትስ ሊሸፍን የሚፈልገው ክልል አለወይ? እንግዲህ አንድ ህግ የሚለውን ለማወቅ ነው ይህ ሁሉ ምርምር: በእርግጥም በጥንቃቄ መረዳቱ ለሎሎች ህይወት ተፅዕኖ መፍጠር የሚያስችል አቅም ነውና ትክክለኛው ሃሳብ ማግኘት ግድያደርገዋል።

በህይወት ውስጥም እውነትን መፈለግ ከዚህ የባሰ ዝርዝር እይታ ይጠይቃክ ። ፊታችን ላይ እየሆነ ያለውን ብቻ ሳይሆን ከዛ አልፈን ማየት ይጠይቃል። ግለሰቦችን በውሳኔዎቻቸው እንዳንፈርፍባቸው ወይም የራሳችን እርምጃዎች ጠባብ በሆነ መንገድ ውስጥ እንዳይገኝ እውነትን መከታተል መልካም ነው።

የሐንስ 8:32 እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል፡ አላቸው።