የመወለዴ ክፍል

ብዙ ጊዜ ወደ አምላካችን ስንጠጋ ወይንም በራልኝ፣ ተረዳሁ ፣ ገብቶኛል እያልን ስንል የገባን ምንአልባትም የጠቅላላውን እውነት ጥቂቱን ብቻ መሆኑን ለማየት ጊዜ ይወስድብናል ወይንም ደግሞ የዛን እይታ ትልቅ ክፍል እንዳለው ለማመን ይከብደናል። እውነቱ ግን ይህ ነው።

ከእውቀት ከፍለን እናውቃለን

ምንም ያክል ሊቅ ጠቢብ ብንሆን ወይንም የሃይማኖት ጥናት ብናደርግ አምላክ ታውቆ አይጨረስም። አምላክ አምላክ ነውና እንክዋን እርሱን በሙሉ አውቆ ለመጨረስ የፈጠረውን አንድ ፍጥረት እንኳን ለማጥናት ዘመናት ይፈጃል። ለዚህ አይደል ሳይንቲስቶች ዛሬም ስራ ያላቸው! ፍጥረት እስካለ የሚጠና ነገር ይኖራልና።

ወደ ተነሳሁበት ልመለስና እውነት እውነት ግን ምን ያክል ነው የበራልን? ምን ያክል ነው የተረዳነው? የአምላክ ልጅ ነኝ ብሎ አንድሰው በምድር እየተመላለሰ ነገርግን አንድም የአባቱ ሁኔታ በእርሱ ላይ መገለጥ ካልቻለ በእርግጥ ልጅ ነው ማለት እንችላለን? ይህን ሁኔታ በምን ገምግመን ነው አዎ የአምላክ ልጅ ነው ማለት የምንችለው? ለምሳሌ አንድ ልጅ አባቱን በመልክ ሊመስል ይችላል ቁርጥ አባቱን ነው ይላሉ የአገሬ ሰዎች። ወይንም የአባቱን ሃብት ያለመከልከል ሲጠቀም ብናይ አለያ ይህ ሰው ጥፋት አጥፍቶ ሲይዝ አባቱ ዋስ ከፍሎ ሲያስፈታው ስናይ ከሌላው ሰው የሚለይበት ነገር እናያከን። ምንአልባትም እንክዋን ያለ አግባብ ያባቱን ሃብት ቢበትን አንተ እንዴት በተንክ ብሎ የሚጠይቅ የውጪ ሃይል የለም። ምክንያቱም ይህ በአባትና ልጅ መካከል የሚደረግ ውይይት ነውና ሌላው ሰው አያገባውም።

ታዲያ ግን ለተቀበሉት ሁሉ ግን በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የልጅነት ስልጣን ሰጣቸው ተብሎ ተፅፎ ሳለ ። ልጅ ነኝ የሚለው ጉዳይ ምንው ለብዙ ዳግም ተወላጅ ቃል ብቻ ሆነ? ለዚህ ነው ጥያቄው ያነሳሁን የተገለጠልን በከፊል ብቻ ነው መሰል? ልጅ ከሆንክ/ሽ አዲስ ዘር ውስጥ ገብተሃል/ሻል። አባት ያለውን ሁሉ ነህ/ሽ።

ይህ እውነት ከሲኦል ማምለጥ አንዱ ጅማሬ ሲሆን ደግሞም አምላክን መምሰል ፍፃሜው ነው። በእነዚህ ሁለት ጥጎች ውስጥ የትኛው ጋር ደርሳችሁ ይሆን?

ኢየሱስም ደግሞ አላቸው፡— እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እኔ የበጎች በር ነኝ።

Then said Jesus unto them again, Verily, verily, I say unto you, I am the door of the sheep.

ዮሐንስ 10:7

ነፃነት Nov, 19 2022

ወደ ኮሌጅ ልጅን መላክ

የሰባት አመት ልጄን የበጋ ወራት የመፅሃፍ ቅዱስ ካምፕ ላደርሰው ሻንጣውን ይዞ ከቤት ስንወጣ ነፍሴ ድንገት ከውስጤ የወጣች መሰለኝ የምንኖርበትን ቤት በር እንክዋን አልዘጋሁም ልጄ ላይ አፍጥጬ ቀረሁ። ጊዜና ቦታ በማይገድበው ምእናብ ልጄን ኮሌጅ ሲሄድ አየሁት ፣ በኮሌጅ ትምህርት ቢዚ ሲሆን ሊያወራኝ እንክዋ ጊዜ የለኝም ሲል። ጊዜ ፍጥነቱ!!

ትምህርት ጨርሶ እቤት ይመጣል ብዬ ላስብ ስሞክር አይ አይደለም ስራ ይይዘዋል ከአገር አገር፣ ከቢሮ ቢሮ፣ ታላላቅ ጉዳዮችን ሊፈፅም ይሮጣል። ልጄ ናፈቀኝ!!

እንዴ እንዴ በቃ እንዲህ ነው ድንገት ሳልዘጋጅ ልጄ ከእጄ የሚወጣው? የልጄ በፍጥነት ማደግ ማስረጃ ሆነው ከፊቴ ተደረደሩ: እውነት ነው ጨቅላ ሆኖ እጄ ላይ የተንከባለለበት ቀን እና ዛሬ የደረሰበት እድሜ በምን ጊዜ እንደደረሰ በትክክል አይገባኝም በጣም ቸኩሎብኛል።

አውቃለሁ ይህ ብላቴና በጎበዝ እጅ እንዳለ ቀስት ነው ተወርውሮ አላማውን ይመታል። ደግሞም ይወጣል ይወርሳል ያሸንፋል።

ለእኔ ግን ዛሬ ናፍቆት በሆዴ ውስጥ ገባ ልጄ እንዳይሄድብኝ ፈለኩ: አይን አይኑን አያለሁ የያዘውን ሻንጣ አያለሁ። ላስቀረው? እድሜው ገናነው ምን አስቸኮለኝ? ይቅር እቤት ውስጥ ይቀመጥ ልቤ አማራጭ ሰጠኝ። አይ ይሄማ ለእድገቱ ውሳኝ ነው ዛሬ ህይወቱ ላይ የዘራሁት ነው ነገ ተፅእኖ የሚያመጣው። ክርክር ውስጥ ገባሁ. “ማም!! ” ልጄ ቀሰቀሰኝ : “በር እየዘጋሁ ነው መጣሁ” መለስኩለት። ምን ሆናለች ዛሬ እናቴ ሳይል አይቀርም አስተያየቱ ያስታውቃል

ተንደርድሬ አቀፍኩት ሳምኩት፣ እወድሃለሁ እሺ እሺ!፣ “እ” መልሱ ነበር። ” ቃል ግባልኝ” ጠያቂ ሆንኩ. “ዋት?” ነገሬ የገረመው ልጄ. “አሁን እኮ ትልቅ ልትሆን ነው ኮሌጅ ልትገባ ልትማር ስራ ልትይዝ በቃ ጊዜ አይኖርህም።” ልጄ የማወራውን በግልፅ ይግባው አይግባው አላውቅም ነገር ግን የልቤን ጭንቀት መተንፈስ ቀጠልኩ። ስለዚህ አደራ እንድትደውልልኝ እሺ “ኖ!! አም ጎነ ቢ ቢዚ” የልጄ መልስ ነበር። “ትናፍቀኛለህ እኮ እባክህ?” “ማም!” ስምንት አመት እንክዋን ካልሞላው ልጄ ጋር ድርድር ያዝኩ ቀኑ ሲደርስ ከማለቅስ በጊዜ ብለምን ይሻለል ብዬ።

ምሳሌ 22: 6 ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም።

በዚህ ውስጥ ነፍሴ ሌላ ነገር አስተዋለች በልዩ ልዩ ነገር ዛሬ ቢዚ ሆኜ የማይመለስ ውድ ጊዜ ከልጄጋር ማሳለፌን እንዳያመልጠኝ ፣ እንድደሰትበት ዋጋ እንድ ሰጠው። ነገ የልጄ ቀን ነው እርሱ ተራውን የሚሮጥበት የሚወርስበት ነውና የእርሱን ጊዜ መሻማት ሳይሆን የእኔን ጊዜ በአግባቡ መጠቀምን ተማርኩ።

እየተነጋገርን አሳንሳር ውስጥ ገብተን መኪናዬ ጋር ደረስን። አምላኬ ታማኝ እና እውነተኛ ነው ታላቅና ሃይለኛ ነገር በዚህ ልጅ ያደርጋል። ቀኑ ሲደርስ እኔንም ይረዳል።

እናንተስ ልጃችሁ የቱጋር ነው ያሉት? የትስ እንዲዱ ታያላችሁ?

ነፃነት

What makes you interested?!

Here are some thoughts, when we were younger anything that our older brother, sister or friend act, say or does keeps our mind for a while. Trying to do exactly what we have seen “monkey see monkey do”. We think its cool we do not process the consequence.

Then we get older success is our drive we want to achieve something. Anything but that can put as in spotlight. So we can showoff! “I did it”. Me is the the center. We plan work hard we make it happen,

Then what? Tuff question now what? Difficult to explain, it seems no one will understand. Things that looks interesting are not interesting any more, thing that looks unreachable are under the foot now: then what?

Have you ever stuck on this moment? May be yes may be not, if you are here welcome to rearranging your vision if you not here yet, wait for it you will get there!

Life is more beautiful and fresh very moment when the center of it is not “ME”. Learn that in life her self, joyful moment are stack with others “WE” bring more fun that me. Together we are Strong, fresh and alive!

Dream for others strive to support be consistent. Some one thought me as a teenage girl the “the secret of greatness is taking responsibility!” It’s stay with me. So find your interest in helping others you will never get bord with it.

Netsanet

The price of greatness is responsibility.” – Winston Churchill.

ስራ ላይ ሆኜ ያገኘኛል

ምን እጃችሁ ላይ አለ? እርሱ እመጣለሁ ብሎ የዘገየ በሚመስለበት በዚህ ሰአት እርሱ የሚከፍለውን ደሞዝ ይዞ ሲመጣ ማንን ያገኝ ይሆን ምንስ በእጅ ላይ ይገኝ ይሆን?

ስራ የተሰጥን እንድናበጅ እንድናስተዳድር ተንከባካቢ እንድንሆን እንድን ጠብቅ ነው ይህ ከሰማይ ያለው ሃሳብ ነው። መስተዳድር ተብሎ በተሰጠህ ላይ ምን ያክል ሰርተህ ይሆን? በአንተ በእንቺ ውስጥ ስራ ግን ምን አይነት ትርጉም ይኖረው ይሆን? ምን አይነትስ ስራስ እየሰራሽ አለቃሽ ያገኝሽ ይሆን?

ገንዘብ መውደድ የሃጥያት ሁሉ ስር ነውና የምናሳድደውን ብናውቅ መልካም ነው ገንዛብ ለማግኘት ፪፬ ሰአት ስትሮጥ ውለህ አድረህ ድንገት የደረስክበት ሲመስልክ ከእጅ አፈትልኮ እንደ ምርጥ እየመሰለ በብዙ ምኞት እና ሃሳብ በማናወዝ ከተፈጠርክለት የመግዛት ስፍራ ያወርድህና ባርያ ያደግሃል። አለቃህንም በትጋት እንዳትጠብቅ ያሳስታል።

ትዳር ብዙ ወገኖኝ በብቸኝነት ዘመናቸው ፈጣን ሯጭ ናቸው ትዳር ውስጥ ሲገባ ቀዝቀዝ ማለት መጀመሩ መልካም ቢመስልም ለብዙዎች ግን ጭልጥ ብሎ መተኛ ይሆናል። ንቃ ንቂ ትዳርሽ በእርግጥ በጌታ ፊት የምትሸለሚበት ቢሆንም የእርሱን ስራ ግን እርግፍ አድርገህ /ሽ እንድትተዊው አልነበረም የሰጠህ።

ድካም በሁሉ ቤት ያንኳኳል ካለብን ጫና ወይም ከወደቀ አለም ግፊያ የተነሳ እርሱም ቢሆን ግን ከመንቃትና ከመጠበቅ አይከለክልም

ምንድን ይሆን ያደከመህ ስራህን እንዳትሰራ ያስደረገህ? እኔ ግን ድንገት በክብሩ ቢገለጥ ስራ ላይ ሆኜ ያገኘኛል አታንቀላፋ አታንቀላፊ ጊዜው በረዘመ ጊዜ ተስፍሽ የበለጠ ይታደድ እንጂ አትዘናጊ።

ዘፍጥረት 1:28                                               እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው፡— ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥ ግዙአትም፤ የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ግዙአቸው።

ነፃነት


			

እግዚአብሔር ሆይ እወድሃለሁ

ይድረስ ለምወድህ እና ለማከብርህ እግዚአብሔር: እኔ ደህና ስለሆንኩና ስለተጠብኩ ብቻ ሳይሆን በሁሉ ላይ ስልጣን ያለህ እንደሆንክ ስለማውቅ በደስታ ይህን እፅፍልሃለሁ።

My letter to you Lord

ለመሆኑ በህይወት መዝገብ ውስጥ ቀላል የሚባል የህይወት ጉዞ አለን? እንደው መንገዱ አልጋ በአልጋ የሆነለት ማን ይሆን? እኔን አይመስለኝም እያንዳንዱ ሰው የሚያልፍበት መንገድ የራሱ ኮረብታ ቁልቁለት ሜዳ ይኖረዋል። ” የ ይስሐቅን ህይወት ተመልክቼ ከ ወገኖቹ አንፃር ሲታይ ቀለል ያለ ህይወት የኖረ ይመስላል ነገርግን በደንብ ሲታይ ብዙ ግፊያ የነበረበት ህይወት ነው ። ማሳረፍን እምታውቅ አንተ ብታሳርፈውም”

በእርግጥ ለአንዳንዶቻችን ከባድ የሚመስሉ መንገዶች ይሰጡን እና እንዴት እንደምናልፋቸው ስንጨነቅ ገና ቀኑ ሳይደርስ ሃይላችንን እንጨርሳለን። የትግስትን ፍሬ ለማየት የቻለ ምንኛ እድለኛ ነው። “የዳዊት ህይወት ያሳዝናል በብዙ ስደት ፣ መገፋት፣ ከሞት ጋር ፍጥጫ ውስጥ ነው። ምንአልባት በነዚህ የስደት ዘመናት ይህ ሰው መጠራቱን መቀባቱን ተጠራጥሮ ይሆናል: የመከራው ርዝመት ተስፋ የሚያስቆርጡ ወቅቶች ጋር መጋፈጡ ቀላል አልነበረም ነገርግን አምላክ ከተናገረው ህይወቱ ላይ ያልተከናወነ አልነበረም ”

እኔ እራሴ ነገር ቀለል ብሎልኝ የኖርኩባቸውን ዘመናት አስብና እንዴት እግዚአብሔር መልካም ነው እላለሁ : በዛው ልክ አላልፍም ብዬ ተስፋ የቆረጥኩባቸው ተራሮች ጋር እፋጠጣለሁ በዚህኛውም እግዚአብሔር መልካም ነው። የተራራው መትለቅ ወይም ማነስ ሳይሆን የአምላክ ማንነቱ ስለሆነ ስልጣን ያለው በዚህ ተስፋ ደስ እሰኛለሁ።

ቆይ ግን ደብዳቤው ለእግዚአብሔር አልነበር እንዴ መፃፍ የጀመርኩት እንዴት ሆኖ ነው የህይወት ውጣ ውረድ መዝገብ ውስጥ የገባሁት ? ለነገሩ ህይወትን እራሱ የያዝከው አንተ ስለሆንክ በውስጡ ያከሁት እኔ የገባኝን ባወራልህ ትክክል እንጂ ስህተት አይሆንም።

You are wrong

Some times until you admit you are wrong you will never get back what you have lost. which ever way you try to justify, it will keep looking back at you. the truth never change.

Most of the time we run away from our failures; we don’t like to look back at them. If it is possible we look for others to blame. children’s like to use “it’s not me” word; which show me the bigger picture of us adults. How many of us take time to see inside and say it could be me. it’s because of the words, actions I choose make this effect, I am responsible for it. the funny thing is we expect children around us to admit they did wrong but we care humongous denial of our mistakes.

But the solution would come only from the ground of facing the truth, looking what has been done wrong, admitting mistakes then ask forgiveness. I don’t think any creation has power to forgive you totally and set you free but the creator dose. You see some people may come and say to you “I forgive you” or you may reflect and forgive yourself; but something keep dragging ‘yes you are not totally free’ you need to come before your creator and admit your were wrong, believe He is willing to forgive you call Him, He is nearer than you think.

once you make the agreement with almighty then let it go. You are for given. it is forgotten in heaven so is in earth; has no power over you, your future. You are redeemed. No one has a right to drag you down. ‘NO ONE’ you are set back to the original place of creation. so go for it strive, win, that is your portion.

Netsanet